Psa 130

? AI
1
አቤቱ፥ አንተን ከጥልቅ ጠራሁህ።
2
አቤቱ፥ ድምፄን ስማ፤ ጆሮህ የልመናዬን ቃል የሚያደምጥ ይሁን።
3
አቤቱ፥ ኃጢአትንስ ብትጠባበቅ፥ አቤቱ፥ ማን ይቆማል?
4
ይቅርታ ከአንተ ዘንድ ነውና።
5
አቤቱ፥ ስለ ስምህ ተስፋ አደረግሁህ፤ ነፍሴ በሕግህ ታገሠች።
6
ከማለዳው ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊት ነፍሴ በእግዚአብሔር ታመነች።
7
ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረት፥ በእርሱም ዘንድ ብዙ ማዳን ነውና እስራኤል በእግዚአብሔር ይታመን።
8
እርሱም እስራኤልን ከኃጢአቱ ሁሉ ያድነዋል።
Global Bible Tools - Collaborative Bible translation platform